Thursday Sep 09

Koromi


Amana Weldach




Amana kids was established to help eliminate some of the deprivations orphan children face in and around Harar. In 1995 we reached out to five kids. Today, we have reached 21 children ranging from kindergarten to seventh Grade. Their ages range between 3 and 15 with complete gender equality. Amana will add an additional 5 to10 kids annually until the future goal of 500 kids is reached.

Harar

 

ለከተሞች የመሠረተ ልማት ፕሮግራም ለ19 ከተሞች የሚውል 150 ሚሊዮን

Attention: open in a new window. PDFPrintE-mail
Repoter: Wednesday, 28 October 2009
በብርቱካን ፈንታ

ለከተሞች የመሠረተ ልማት ማስፋፊያና አቅም ግንባታ ፕሮግራም ለ19 ከተሞች  የሚውል 150 ሚሊዮን ዶላር የዓለም ባንክ ብድር መስጠቱን የሥራና ከተማ ልማት ሚኒስቴር ገለፀ፡፡፡
 በአዲስ አበባ ከተማ ከጥቅምት 13 እስከ ጥቅምት 16 ቀን 2002 ዓ.ም. በተለያዩ ዝግጅቶች ሲከበር የቆየውን የከተሞች ቀንን መጠናቀቅን አስመልክቶ በሥራና ከተማ ልማት ቢሮ የፖሊሲ ጥናትና ዕቅድ ማስተባበሪያ ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር አብርሃም ተከስተ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ እንደገለፁት በተገኘው ብድር አዲስ አበባ፣ ድሬዳዋና ሐረርን ጨምሮ በአራቱም ክልሎች የሚገኙ አራት ከተሞች ተጠቃሚ እንደሚሆኑ ተናግረዋል፡፡

ገንዘቡ አዲስ አበባ፣ ድሬዳዋ እና ሐረርን ጨምሮ ከአማራ ክልል፣ ባሕርዳር፣ ጐንደር፣ ደሴና ኮምቦልቻ፣ ከኦሮሚያ አዳማ፣ ቢሾፍቱ፣ ሻሸመኔና ጅማ፣ ከትግራይ መቀሌ፣ አዲግራት፣ ሽሬና አክሱም እንዲሁም ከደቡብ ክልል አርባምንጭ፣ ሶዶ፣ ዲላና ሐዋሣ መሆናቸውን ዶ/ር አብርሃም ተናግረዋል፡፡

ከባንኩ ከተገኘው ብድር በተጨማሪ “እያንዳንዳቸው ከተሞች 20 ከመቶ ማዋጣት  ይጠበቅባቸዋል” ያሉት ኃላፊው ገንዘቡ የሚውለው ለከተማ መሠረተ ልማትና አገልግሎት ተብለው ለተለዩ ሥራዎች ሲሆን የአስፋልት ሥራን እንደማያጠቃልል  ከከተሞቹ ጋር መስማማታቸውን አክለው ገልፀዋል፡፡

“ለበዓሉ ምን ያህል ወጪ አውጥታችኋል?” ተብሎ ከጋዜጠኞች ለቀረበላቸው ጥያቄ ኃላፊው ሲመልሱ “ጥቃቅንና አነስተኛ ወጪ ያለው ዝግጅት ነው የተደረገው፡፡ በተጋነነ ወጪ የተከበረ ቀን አይደለም” በማለት ጥያቄውን አድበስብሰውት አልፈዋል፡፡

የከተሞች ቀን ለአራት ተከታታይ ቀናት ለመጀመሪያ ጊዜ በአዲስ አበባ ከተማ የተከበረ መሆኑን የገለፁት ዶ/ር አብርሃም፣ ዓላማውም የከተማ ነዋሪዎችንና ባለ ድርሻ አካላትን ተሳትፎ በማጠናከርና መልካም ተሞክሮዎችን ማስፋፋት መሆኑን ተናግረዋል፡፡

ለመጀመሪያ ጊዜ በተከበረው የከተሞች ቀን የተለያዩ ነገሮች መደረጋቸውን የገለፁት ኃላፊው፤ የከተሞች ትብብር መድረክ ጥቅምት 12 ቀን 2002 ዓ.ም. መመስረቱንና አዲስ አበባ ከተማ የትብብር መድረኩ ሊቀመንበር ሆና መመረጧን፤ 43 ከተሞች መሳተፋቸውን፣ በተለያዩ ገቢሮች ከተሞች ተወዳድረው አሸናፊዎቹ መሸለማቸውን አስታውሰዋል፡፡

Translate



My Favorite Video

mod_vvisit_countermod_vvisit_countermod_vvisit_countermod_vvisit_countermod_vvisit_countermod_vvisit_countermod_vvisit_counter
mod_vvisit_counterToday344
mod_vvisit_counterYesterday849